ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ሳሙኤል 22:29-38 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ መብራቴ ነህ፤ እግዚአብሔርም ጨለማዬን ያበራል።

30. በአንተ ርዳታ በጠላት ሰራዊት ላይ ወደፊት ገፍቼ እሄዳለሁ፤ በአምላኬም ኀይል ቅጥሩን እዘላለሁ።

31. “የአምላክ መንገዱ ፍጹም ነው፤ የእግዚአብሔርም ቃል የነጠረ ነው፤ለሚታመኑበትም ሁሉ ጋሻ ነው፤

32. ከእግዚአብሔር በቀር አምላክ ማን አለና፤ከአምላካችንስ በቀር ዐለት ማን ነው?

33. ኀይልን የሚያስታጥቀኝ፣መንገዴንም የሚያቀና እርሱ አምላኬ ነው።

34. እግሮቼን እንደ ብሆር እግር ያበረታል፤በከፍታዎችም ላይ አጽንቶ ያቆመኛል።

35. እጆቼን ለጦርነት ያሰለጥናል፤ክንዶቼም የናስ ቀስት ይገትራሉ።

36. የማዳንህን ጋሻ ሰጥተኸኛል፤ድጋፍህ ታላቅ አድርጎኛል።

37. እርምጃዬን አሰፋህ፤እግሮቼም አልተሰነካከሉም።

38. “ጠላቶቼን አሳደድሁ፤ አጠፋኋቸውም፤እስኪደመሰሱም ድረስ ወደ ኋላ አልተመለስሁም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ሳሙኤል 22