ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 4:5-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ቀንና ሌሊት ትደናበራላችሁ፤ነቢያትም ከእናንተ ጋር ይደናበራሉ፤ስለዚህ እናታችሁን አጠፋታለሁ፤

6. ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል።“ዕውቀትን ስለናቃችሁ፣እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤የአምላካችሁን ሕግ ስለ ረሳችሁ፣እኔም ልጆቻችሁን እረሳለሁ።

7. ካህናት በበዙ ቊጥር፣በእኔ ላይ የሚያደርጉት ኀጢአት በዝቶአል፤ክብራቸውንም በውርደት ለውጠዋል።

8. የሕዝቤ ኀጢአት ለመብል ሆኖላቸዋል፤ርኵሰታቸውንም እጅግ ወደዱ።

9. ካህናትም ከሕዝቡ የተለዩ አይደሉም፤ሁሉንም እንደ መንገዳቸው እቀጣቸዋለሁ፤እንደ ሥራቸውም እከፍላቸዋለሁ።

10. “ይበላሉ ግን አይጠግቡም፤ያመነዝራሉ ግን አይበዙም፤ እግዚአብሔርን በመተው፣ራሳቸውን

11. ለአመንዝራነት፣ለአሮጌና ለአዲስ የወይን ጠጅ አሳልፈው ሰጡ፤በእነዚህም

12. የሕዝቤ ማስተዋል ተወሰደ፤ከዕንጨት የተሠራውን ጣዖት ምክር ይጠይቃሉ፤ዘንጋቸውም ይመልስላቸዋል።የአመንዝራነት መንፈስ ያስታቸዋል፤ለአምላካቸውም ታማኝ አልሆኑም።

13. በተራሮችም ጫፍ ላይ ይሠዋሉ፤መልካም ጥላ ባለው፣ በባሉጥ፣በኮምቦልና በአሆማ ዛፍ ሥር፣በኰረብቶችም ላይ የሚቃጠል ቊርባን ያቀርባሉ።ስለዚህ ሴቶች ልጆቻችሁ ዘማዊ፣ምራቶቻችሁም አመንዝራ ይሆናሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሆሴዕ 4