ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 103:1-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪየውስጥ ሰውነቴም ሁሉ ቅዱስ ስሙን ባርኪ።

2. ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ፤ውለታውንም ሁሉ አትርሺ፤

3. ኀጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፣ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፣

4. ሕይወትሽን ከጥፋት ጒድጓድ የሚያድን፣ምሕረትንና ርኅራኄን የሚያቀዳጅሽ፣

5. ጐልማሳነትሽም እንደ ንስር ይታደስ ዘንድ፣ምኞትሽን በበጎ ነገር የሚያረካ እርሱ ነው።

6. እግዚአብሔር ለተጨቈኑ ሁሉ፣ቅን ፍርድንና ፍትሕን ይሰጣቸዋል።

7. መንገዱን ለሙሴ፣ሥራውንም ለእስራኤል ሕዝብ አሳወቀ።

8. እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ፣ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩም የበዛ ነው።

9. እርሱ ሁል ጊዜ በደልን አይከታተልም፤ለዘላለምም አይቈጣም።

10. እንደ ኀጢአታችን አልመለሰልንም፤እንደ በደላችንም አልከፈለንም።

11. ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፣እንዲሁ ለሚፈሩት ምሕረቱ ታላቅ ናት።

12. ምሥራቅ ከምዕራብ እንደሚርቅ፣መተላለፋችንን በዚያው መጠን ከእኛ አስወገደ።

13. አባት ለልጆቹ እንደሚራራ፣ እግዚአብሔር ለሚፈሩት እንዲሁ ይራራል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 103