ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 104:11-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. የዱር እንስሳትም ከዚያ ይጠጣሉ፤የሜዳ አህዮችም ጥማቸውን ይቈርጣሉ።

12. የሰማይ ወፎች ጎጇቸውን በወንዞቹ ዳር ይሠራሉ፤በቅርንጫፎችም መካከል ይዘምራሉ።

13. ከላይ ከእልፍኝህ ተራሮችህን ታጠጣለህ፤ምድርም በሥራህ ፍሬ ትረካለች።

14. ከምድር ምግብን ታወጣ ዘንድ፣ለእንስሳት ሣርን፣ለሰው ልጆች ሥራ ዕፀዋትን ታበቅላለህ፤

15. የሰውን ልብ ደስ የሚያሰኝ ወይን፣ፊቱን የሚያወዛ ዘይት፣ልቡን የሚያበረታ እህል በዚህ ይገኛል።

16. ደግሞም የእግዚአብሔር ዛፎች፣እርሱ የተከላቸውም የሊባኖስ ዝግባዎች ጠጥተው ይረካሉ፤

17. ወፎች ጎጆአቸውን በዚያ ይሠራሉ፤ሽመላ በጥዶቹ ውስጥ ማደሪያ ታገኛለች።

18. ረጃጅሙ ተራራ የዋልያ መኖሪያ፣የዐለቱም ዋሻዎች የሽኮኮ መሸሸጊያ ናቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 104