ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 104:23-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. ሰውም ወደ ሥራው ይሄዳል፤እስኪመሽም በተግባሩ ላይ ይሰማራል።

24. እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ብዙ ነው!ሁሉን በጥበብ ሠራህ፤ምድርም በፍጥረትህ ተሞላች።

25. ይህች ባሕር ሰፊና የተንጣለለች ናት፤ታላላቅና ታናናሽ እንስሳት፣ስፍር ቍጥር የሌላቸውም ነፍሳት በውስጧ አሉ።

26. መርከቦች በላይዋ ይመላለሳሉ፤አንተ የፈጠርኸውም ሌዋታን በውስጧ ይፈነጫል።

27. ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸው ዘንድ፣እነዚህ ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ።

28. በሰጠሃቸውም ጊዜ፣አንድ ላይ ያከማቻሉ፤እጅህንም ስትዘረጋ፣በመልካም ነገር ይጠግባሉ።

29. ፊትህን ስትሰውር፣በድንጋጤ ይሞላሉ፤እስትንፋሳቸውንም ስትወስድባቸው ይሞታሉ፤ወደ ዐፈራቸውም ይመለሳሉ።

30. መንፈስህን ስትልክ፣እነርሱ ይፈጠራሉ፤የምድርንም ገጽ ታድሳለህ።

31. የእግዚአብሔር ክብር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር፤ እግዚአብሔር በሥራው ደስ ይበለው፤

32. እርሱ ምድርን ሲመለከት፣ ትንቀጠቀጣለች፤ተራሮችም እርሱ ሲዳስሳቸው ይጤሳሉ።

33. በሕይወት ሳለሁ ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ቆሜ እስከ ሄድሁ ድረስም አምላኬን እወድሳለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 104