1. እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤ሥራውንም በሕዝቦች መካከል ግለጡ።
2. ተቀኙለት፤ ዘምሩለት፤ድንቅ ሥራዎቹንም ሁሉ ተናገሩ።
3. በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚሹት ልባቸው ደስ ይበለው።
4. እግዚአብሔርንና ብርታቱን ፈልጉ፤ፊቱንም ዘወትር ፈልጉ።
5. ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣ታምራቱንና ከአፉ የወጣውን ፍርድ አስቡ፤
6. እናንተ የአገልጋዩ የአብርሃም ዘሮች፣ለራሱም የመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤ አስታውሱ።