ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 105:13-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. ከሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲንከራተቱ፣ከአንዱ መንግሥት ወደ ሌላው ሲቅበዘበዙ፣

14. ማንም ግፍ እንዲፈጽምባቸው አልፈቀደም፤ስለ እነርሱም ነገሥታትን እንዲህ ሲል ገሠጸ፤

15. “የቀባኋቸውን አትንኩ፤በነቢያቴም ላይ ክፉ አታድርጉ።”

16. በምድሪቱ ላይ ራብን ጠራ፤የምግብንም አቅርቦት ሁሉ አቋረጠ፤

17. በባርነት የተሸጠውን ሰው፣ዮሴፍን ከእነርሱ አስቀድሞ ላከ።

18. እግሮቹ በእግር ብረት ተላላጡ፤በዐንገቱም የብረት ማነቆ ገባ።

19. የተናገረው ቃል እስኪፈጸምለት፣ የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው።

20. ንጉሥ ልኮ አስፈታው፤የሕዝቦችም ገዥ ነጻ አወጣው።

21. የቤቱ ጌታ፣የንብረቱም ሁሉ አስተዳዳሪ አደረገው፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 105