ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 105:15-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. “የቀባኋቸውን አትንኩ፤በነቢያቴም ላይ ክፉ አታድርጉ።”

16. በምድሪቱ ላይ ራብን ጠራ፤የምግብንም አቅርቦት ሁሉ አቋረጠ፤

17. በባርነት የተሸጠውን ሰው፣ዮሴፍን ከእነርሱ አስቀድሞ ላከ።

18. እግሮቹ በእግር ብረት ተላላጡ፤በዐንገቱም የብረት ማነቆ ገባ።

19. የተናገረው ቃል እስኪፈጸምለት፣ የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው።

20. ንጉሥ ልኮ አስፈታው፤የሕዝቦችም ገዥ ነጻ አወጣው።

21. የቤቱ ጌታ፣የንብረቱም ሁሉ አስተዳዳሪ አደረገው፤

22. ይኸውም ሹማምቱን በራሱ መንገድ ይመራ ዘንድ፣ታላላቆቹንም ጥበብ ያስተምር ዘንድ ነበር።

23. እስራኤል ወደ ግብፅ ገባ፤ያዕቆብ በካም ምድር መጻተኛ ሆነ።

24. እግዚአብሔር ሕዝቡን እጅግ አበዛ፤ከጠላቶቻቸውም ይልቅ አበረታቸው፤

25. ሕዝቡን እንዲጠሉ፣በባሪያዎቹም ላይ እንዲያሤሩ ልባቸውን ለወጠ።

26. ባሪያውን ሙሴን፣የመረጠውንም አሮንን ላከ።

27. እነርሱም ታምራታዊ ምልክቶችን በመካከላቸው፣ድንቅ ነገሮቹንም በካም ምድር አደረጉ።

28. ጨለማን ልኮ ምድሪቱን ጽልመት አለበሰ፤እነርሱም በቃሉ ላይ ማመፅን ተዉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 105