ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 106:12-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ከዚህ በኋላ የተስፋ ቃሉን አመኑ፤በዝማሬም አመሰገኑት።

13. ነገር ግን ያደረገውን ወዲያውኑ ረሱ፤በምክሩም ለመሄድ አልታገሡም።

14. በምድረ በዳ እጅግ መመኘት አበዙ፤በበረሓም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት።

15. እርሱም የለመኑትን ሰጣቸው፤ዳሩ ግን የሚያኰሰምን ሕመም ሰደደባቸው።

16. በሰፈር በሙሴ ላይ፣ ለእግዚአብሔር በተቀደሰውም በአሮን ላይ ቀኑ።

17. ምድር ተከፍታ ዳታንን ዋጠች፤የአቤሮንን ወገን ሰለቀጠች።

18. እሳት በጉባኤያቸው መካከል ነደደ፤ነበልባሉም ክፉዎችን ፈጅቶ አስወገደ።

19. በኮሬብ ጥጃ ሠሩ፤ቀልጦ ለተሠራ ምስልም ሰገዱ።

20. ክብራቸው የሆነውንም ሣር በሚበላ፣በበሬ ምስል ለወጡ።

21. በግብፅ ታላቅ ነገር ያደረገውን፣ያዳናቸውን አምላክ ረሱ፤

22. እርሱ ግን በካም ምድር ድንቅ ሥራ፣በቀይ ባሕርም አስደናቂ ነገር አደረገ።

23. ስለዚህ በመቅሠፍቱ እንዳያጠፋቸው ይመለስ ዘንድ፣እርሱ የመረጠው ሙሴ በመካከል ገብቶ፣በፊቱ ባይቆም ኖሮ፣እንደሚያጠፋቸው ተናግሮ ነበር።

24. ከዚያም በኋላ መልካሚቱን ምድር ናቁ፤የተስፋ ቃሉንም አላመኑም።

25. በድንኳኖቻቸው ውስጥ አጒረመረሙ፤ የእግዚአብሔርንም ድምፅ አላዳመጡም።

26. በምድረ በዳ ሊጥላቸው፣እጁን አንሥቶ ማለ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 106