ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 107:16-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. እርሱ የናሱን በሮች ሰብሮአልና፤የብረቱንም መወርወሪያ ቈርጦአል።

17. አንዳንዶቹ ከዐመፃቸው የተነሣ ቂሎች ሆኑ፤ከበደላቸው የተነሣ ችግር ውስጥ ገቡ።

18. ሰውነታቸው የምግብ ዐይነት ሁሉ ተጸየፈች፤ወደ ሞትም ደጆች ቀረቡ።

19. በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

20. ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው፤ከመቃብርም አፋፍ መለሳቸው።

21. እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

22. የምስጋናም መሥዋዕት ያቅርቡለት፤ሥራውንም ደስ በሚል ዝማሬ ይግለጹ።

23. አንዳንዶቹ በመርከብ ወደ ባሕር ወረዱ፤በታላቅም ውሃ ላይ ሥራቸውን አከናወኑ፤

24. የእግዚአብሔርን ሥራ በዚያ አዩ፤ድንቅ አድራጎቱንም በጥልቁ ውስጥ ተመለከቱ።

25. እርሱ ተናግሮ ዐውሎ ነፋስን አስነሣ፤ነፋሱም ማዕበሉን ከፍ ከፍ አደረገ።

26. ወደ ሰማይ ወጡ፤ ወደ ጥልቅም ወረዱ፤ከመከራቸውም የተነሣ ሐሞታቸው ፈሰሰ።

27. እንደ ሰከረ ሰው ዞሮባቸው ወዲያ ወዲህ ተንገዳገዱ፤መላው ጠፍቶባቸው የሚያደርጉትን አጡ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 107