ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 107:8-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ፣ለሰው ልጆችም ስላደረገው ድንቅ ሥራ ያመስግኑት፤

9. እርሱ የተጠማችውን ነፍስ አርክቶአልና፤የተራበችውንም ነፍስ በበጎ ነገር አጥግቦአል።

10. አንዳንዶቹ በብረት ሰንሰለት ታስረው የተጨነቁ፣በጨለማ፣ በጥልማሞት ውስጥ የተቀመጡ ነበሩ፤

11. በእግዚአብሔር ቃል ላይ በማመፅ፣የልዑልን ምክር አቃለዋልና።

12. ስለዚህ በጒልበት ሥራ ልባቸውን አዛለ፤ተዝለፈለፉ፤ የሚደግፋቸውም አልነበረም።

13. በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው።

14. ከጨለማና ከጥልማሞት አወጣቸው፤እስራታቸውንም በጠሰላቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 107