ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 118:14-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤አዳኝ ሆነልኝ።

15. በጻድቃን ድንኳን የእልልታና የሆታ ድምፅ፣እንዲህ እያለ ያስተጋባል፤“የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች፤

16. የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለች፤ የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች።

17. ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤ የእግዚአብሔርንም ሥራ ገና እናገራለሁ።

18. መገሠጹን እግዚአብሔር እጅግ ገሥጾኛል፤ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።

19. የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤በዚያ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።

20. ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤ጻድቃን በእርሷ በኩል ይገባሉ።

21. ሰምተህ መልሰህልኛልና፣አዳኝም ሆነህልኛልና አመሰግንሃለሁ።

22. ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 118