ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 139 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ሁሉን ዐዋቂ አምላክ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ መረመርኸኝ፤ደግሞም ዐወቅኸኝ።

2. አንተ መቀመጤንና መነሣቴን ታውቃለህ፤የልቤንም ሐሳብ ገና ከሩቁ ታስተውላለህ።

3. መሄድ መተኛቴን አጥርተህ ታውቃለህ፤መንገዶቼንም ሁሉ ተረድተሃቸዋል።

4. እግዚአብሔር ሆይ፤ ገና ቃል ከአንደበቴ ሳይወጣ፣እነሆ፤ አንተ ሁሉንም ታውቃለህ።

5. አንተ ከኋላም ከፊትም ዙሪያዬን ከለልኸኝ፤እጅህንም በላዬ አደረግህ።

6. እንዲህ ያለው ዕውቀት ለኔ ድንቅ ነው፤ልደርስበትም የማልችል ከፍ ያለ ነው።

7. ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ?ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?

8. ወደ ሰማይ ብወጣ፣ አንተ በዚያ አለህ፤መኝታዬንም በሲኦል ባደርግ በዚያ ትገኛለህ።

9. በንጋት ክንፍ ተነሥቼ ብበር፣እስከ ባሕሩ ዳርቻ መጨረሻ ብሄድ፣

10. በዚያም ቢሆን እጅህ ትመራኛለች፤ቀኝ እጅህም አጥብቃ ትይዘኛለች።

11. እኔም፣ “ጨለማው በርግጥ ይሰውረኛል፤በዙሪያዬ ያለውም ብርሃን ሌሊት ይሆናል” ብል፣

12. ጨለማ የአንተን ዐይን አይዝም፤ሌሊቱም እንደ ቀን ያበራል፤ጨለማም ብርሃንም ለአንተ አንድ ናቸውና።

13. አንተ ውስጣዊ ሰውነቴን ፈጥረሃልና፤በእናቴም ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ።

14. ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ሥራህ ድንቅ ነው፤ነፍሴም ይህን በውል ተረድታለች።

15. እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፣ዐጥንቶቼ ከአንተ አልተደበቁም፤በምድር ጥልቀት ውስጥ በጥበብ በተሠራሁ ጊዜ፣

16. ዐይኖችህ ገና ያልተበጀውን አካሌን አዩ፤ለእኔ የተወሰኑልኝም ዘመናት፣ገና አንዳቸው ወደ መኖር ሳይመጡ፣በመጽሐፍ ተመዘገቡ።

17. አምላክ ሆይ፤ ለእኔ ያለህ ሐሳብ እንዴት ክቡር ነው!ቍጥሩስ ምንኛ ብዙ ነው!

18. ልቍጠራቸው ብል፣ከአሸዋ ይልቅ ይበዙ ነበር።ተኛሁም ነቃሁም፣ገና ከአንተው ጋር ነኝ።

19. አምላክ ሆይ፣ ክፉዎችን ብትገድላቸው ምናለበት!ደም የተጠማችሁ ሰዎች ሆይ፤ከእኔ ራቁ!

20. ስለ አንተ በክፋት ይናገራሉና፤ጠላቶችህም ስምህን በከንቱ ያነሣሉ።

21. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚጠሉህን አልጠላምን?በአንተ ላይ የሚነሡትንስ አልጸየፍምን?

22. በፍጹም ጥላቻ ጠልቻቸዋለሁ፤ባላጋራዎቼም ሆነዋል።

23. እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ፤ፈትነኝ፤ ሐሳቤንም ዕወቅ፤

24. የክፋት መንገድ በውስጤ ቢኖር እይ፤በዘላለምም መንገድ ምራኝ።