ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 145:6-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ስለ ድንቅ ሥራህ ብርታት ይነጋገራሉ፤እኔም ስለ ታላቅነትህ ዐውጃለሁ።

7. የበጎነትህን ብዛት በደስታ ያወሳሉ፤ስለ ጽድቅህም በእልልታ ይዘምራሉ።

8. እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው፤ለቍጣ የዘገየ፣ ምሕረቱ የበዛ።

9. እግዚአብሔር ለሁሉ ቸር ነው፤ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው።

10. እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍጥረትህ ሁሉ ያመሰግንሃል፤ቅዱሳንህም ይባርኩሃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 145