ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 17:4-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ከሰዎች ተግባር፣በከንፈርህ ቃል፣ከዐመፀኞች መንገድ፣ራሴን ጠብቄአለሁ።

5. አረማመዴ በመንገድህ ጸንቶአል፤እግሮቼም አልተንሸራተቱም።

6. አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ አንተን እጣራለሁ፤ጆሮህን ወደ እኔ ጣል አድርገህ ጸሎቴን ስማ።

7. ከጠላቶቻቸው መተገኛ ያደረጉህን፣በቀኝ እጅህ የምትታደግ ሆይ፤ጽኑ ፍቅርህን ድንቅ አድርገህ ግለጥ።

8. እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤

9. ከሚያስጨንቁኝ ከክፉዎች፣ከሚከብቡኝ አደገኛ ባላንጣዎቼ ጋርደኝ።

10. ደንዳና ልባቸውን ደፈኑት፤በአፋቸውም ትዕቢት ይናገራሉ።

11. አሳደው ደረሱብኝ፤ ከበቡኝም፤መሬት ላይ ሊዘርሩኝም አፈጠጡብኝ።

12. እነርሱ ለንጥቂያ እንደሚጓጓ አንበሳ፣በስውርም እንደሚያደባ ደቦል አንበሳ ናቸው።

13. እግዚአብሔር ሆይ፤ ተነሥተህ ግጠማቸውና ጣላቸው፤በሰይፍህም ከክፉዎች ታደገኝ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 17