ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 18:29-41 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. በአንተ ጒልበት በሰራዊት ላይ እረማመዳለሁ፤በአምላኬም ኀይል ቅጥር እዘላለሁ።

30. የአምላክ መንገድ ፍጹም ነው፤ የእግዚአብሔር ቃል የነጠረ ነው።መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ፣እርሱ ጋሻ ነው።

31. ከእግዚአብሔር በቀር ማን አምላክ አለ?ከአምላካችንስ በቀር ዐምባ ማን ነው?

32. ኀይልን የሚያስታጥቀኝ፣መንገዴንም የሚያቃና እግዚአብሔር ነው።

33. እርሱ እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች ያደርጋል፤በከፍታዎችም ላይ ያቆመኛል።

34. እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናቸዋል፤ክንዴም የናስ ቀስት መገተር ይችላል።

35. የድል ጋሻ ሰጥተኸኛል፤ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች፤ዝቅ ብለህም ከፍ አደረግኸኝ።

36. ከሥሬ ያለውን ስፍራ ለአረማመዴ አሰፋህልኝ፤እግሬም አልተንሸራተተም።

37. ጠላቶቼን አሳድጄ ያዝኋቸው፤እስኪጠፉም ወደ ኋላዬ አልተመለስሁም።

38. እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቀቅኋቸው፤ከእግሬም ሥር ወደቁ።

39. አንተ ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፤ባላንጦቼ እግሬ ላይ እንዲደፉ አደረግህ።

40. ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው እንዲሸሹ አደረግህ፤እኔም የሚጠሉኝን አጠፋኋቸው።

41. ለርዳታ ጮኹ፤ የሚያስጥላቸው ግን አላገኙም፤ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም አልመለሰላቸውም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 18