ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 18:39-45 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

39. አንተ ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፤ባላንጦቼ እግሬ ላይ እንዲደፉ አደረግህ።

40. ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው እንዲሸሹ አደረግህ፤እኔም የሚጠሉኝን አጠፋኋቸው።

41. ለርዳታ ጮኹ፤ የሚያስጥላቸው ግን አላገኙም፤ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም አልመለሰላቸውም።

42. ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ አደቀቅኋቸው፤እንደ መንገድ ላይ ጭቃም አውጥቼ ጣልኋቸው።

43. ከሕዝብ ግርግር አወጣኸኝ፤የሕዝቦች መሪ አድርገህ አስቀመጥኸኝ፤የማላውቀውም ሕዝብ ተገዛልኝ።

44. ትእዛዜን እንደ ሰሙ ይታዘዙልኛል፤ባዕዳንም በፊቴ አንገት ደፉ።

45. ባዕዳን በፍርሃት ተዋጡ፤ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 18