ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 18:42-49 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

42. ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ አደቀቅኋቸው፤እንደ መንገድ ላይ ጭቃም አውጥቼ ጣልኋቸው።

43. ከሕዝብ ግርግር አወጣኸኝ፤የሕዝቦች መሪ አድርገህ አስቀመጥኸኝ፤የማላውቀውም ሕዝብ ተገዛልኝ።

44. ትእዛዜን እንደ ሰሙ ይታዘዙልኛል፤ባዕዳንም በፊቴ አንገት ደፉ።

45. ባዕዳን በፍርሃት ተዋጡ፤ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ።

46. እግዚአብሔር ሕያው ነው! ዐምባዬ ይባረክ፤ያዳነኝ አምላክ ከፍ ከፍ ይበል።

47. እርሱ በቀሌን የሚመልስልኝ፣ሕዝቦችንም የሚያስገዛልኝ አምላክ ነው፤

48. ከጠላቶቼም የሚታደገኝ እርሱ ነው።አንተ ከባላንጦቼ በላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ፤ከጨካኞች አዳንኸኝ።

49. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለዚህ በአሕዛብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤ስምህንም በመዝሙር እወድሳለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 18