ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 24:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ምድርና በእርሷ ያለው ሁሉ፣ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉ የእግዚአብሔር ነው፤

2. እርሱ በባሕሮች ላይ መሥርቶአታልና፤በውሆችም ላይ አጽንቶአታል።

3. ወደ እግዚአብሔር ተራራ ማን ሊወጣ ይችላል?በተቀደሰ ስፍራውስ ማን ይቆማል?

4. ንጹሕ እጅና ቅን ልብ ያለው፤ነፍሱን ለሐሰት ነገር የማያስገዛ፤በውሸት የማይምል፤

5. እርሱ በረከትን ከእግዚአብሔር ዘንድ፣ምሕረትንም ከአዳኝ አምላኩ ይቀበላል።

6. እርሱን የሚፈልግ ትውልድ እንዲህ ነው፤የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ፊትህን የሚፈልግ እንዲህ ያለ ነው። ሴላ

7. እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤እናንተ የዘላለም በሮች፤የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!

8. ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው? እግዚአብሔር ነው ብርቱና ኀያል፤ እግዚአብሔር ነው በውጊያ ኀያል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 24