ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የተጨቈነ ሰው ጸሎት

የዳዊት መዝሙር

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚታገሉኝን ታገላቸው፤የሚዋጉኝንም ተዋጋቸው።

2. ትልቁንና ትንሹን ጋሻ ያዝ፤እኔንም ለመርዳት ተነሥ።

3. በሚያሳድዱኝ ላይ፣ጦርና ጭሬ ምዘዝ፤ነፍሴንም፣“የማድንሽ እኔ ነኝ” በላት።

4. ሕይወቴን የሚፈልጓት፣ይቅለሉ፣ ይዋረዱ፤እኔን ለማጥፋት የሚያሤሩ፣ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።

5. በነፋስ ፊት እንዳለ እብቅ ይሁኑ፤ የእግዚአብሔር መልአክ ያሳዳቸው።

6. መንገዳቸው ጨለማና ድጥ ይሁን፤ የእግዚአብሔር መልአክ ያባራቸው።

7. ያለ ምክንያት ወጥመዳቸውን በስውር አስቀምጠውብኛልና፤ያለ ምክንያት ለነፍሴ ጒድጓድ ቈፍረውላታል።

8. ያልታሰበ ጥፋት ይምጣባቸው፤የሰወሩት ወጥመድ ይያዛቸው፤ይጠፉም ዘንድ ወደ ጒድጓዱ ይውደቁ።

9. ነፍሴም በእግዚአብሔር ደስ ይላታል፤በማዳኑም ሐሤት ታደርጋለች።

10. የሠራ አካላቴ እንዲህ ይልሃል፤“እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ማን አለ?ድኻውን ከእርሱ ከሚበረቱ፣ችግረኛውንና ምስኪኑን ከቀማኞች ታድናለህ”።

11. ጨካኝ ምስክሮች ተነሡ፤ስለማላውቀውም ነገር ጠየቁኝ።

12. በበጎ ፈንታ ክፉ መለሱልኝ፤ነፍሴንም ብቸኛ አደረጓት።

13. እኔ ግን እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ፤ነፍሴንም በጾም አደከምኋት፤ጸሎቴም መልስ አጥቶ ወደ ጒያዬ ተመለሰ።

14. ለወዳጄ ወይም ለወንድሜ እንደማደርግ፣እየተንቈራጠጥሁ አለቀስሁ፤ለእናቴም እንደማለቅስ፣በሐዘን ዐንገቴን ደፋሁ።

15. እነርሱ ግን እኔ ስሰናከል በእልልታ ተሰበሰቡ፤ግፈኞች በድንገት ተሰበሰቡብኝ፤ያለ ዕረፍትም ቦጫጨቁኝ።

16. እንደ ምናምንቴዎች አፌዙብኝ፤ጥርሳቸውንም አፋጩብኝ።

17. ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ ዝም ብለህ ታያለህ?ነፍሴን ከክፉ ሥራቸው፣ብርቅ ሕይወቴን ከአንበሶች ታደጋት።

18. በታላቅ ጉባኤ መካከል አመሰግንሃለሁ፤ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበትም አወድስሃለሁ።

19. ከምድር ተነሥተው ጠላቶቼ የሆኑት፣በላዬ ደስ አይበላቸው፤እንዲያው የሚጠሉኝ፣በዐይናቸው አይጣቀሱብኝ።

20. የሰላም ንግግር ከአፋቸው አይወጣም፤ዳሩ ግን በምድሪቱ በጸጥታ በሚኖሩት ላይ፣ነገር ይሸርባሉ።

21. አፋቸውን አስፍተው ከፈቱብኝ፤“ዕሠይ! ዕሠይ! በዐይናችን አየነው” አሉ።

22. እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን አይተሃልና ዝም አትበል፤ጌታ ሆይ፤ ከእኔ አትራቅ።

23. አምላኬ፣ ጌታዬ፤ ለእኔ ለመሟገት ተነሥ!ልትከራከርልኝም ተንቀሳቀስ።

24. እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ በጽድቅህ ፍረድልኝ፤በእኔም ላይ ደስ አይበላቸው።

25. በልባቸው፣ “ዕሠይ! ያሰብነው ተሳካ!ዋጥ አደረግነውም” አይበሉ።

26. በጭንቀቴ ደስ የሚላቸው፣ይፈሩ፤ ግራም ይጋቡ፤በእኔ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ፣ዕፍረትንና ውርደትን ይከናነቡ።

27. ፍትሕ ማግኘቴን የሚወዱ፣እልል ይበሉ፤ ሐሤትም ያድርጉ፤ዘወትርም፣ “የባርያው ሰላም ደስ የሚለው፣ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል!” ይበሉ።

28. አንደበቴ ጽድቅህን፣ምስጋናህንም ቀኑን ሙሉ ይናገራል።