ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የጻድቁና የክፉው ዕጣ ፈንታ

የዳዊት መዝሙር

1. ዐመፀኞችን በማየት አትሸበር፤በክፉ አድራጊዎችም አትቅና፤

2. እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፤እንደ ለምለም ቅጠልም ይጠወልጋሉ።

3. በእግዚአብሔር ታመን፤ መልካምንም አድርግ፤በምድሪቱ ተቀመጥ፤ ዘና ብለህ ተሰማራ።

4. በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፤የልብህንም መሻት ይሰጥሃል።

5. መንገድህን ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤በእርሱ ታመን፤ እርሱም ያከናውንልሃል፤

6. ጽድቅህን እንደ ብርሃን፣ያንተን ፍትሕ እንደ ቀትር ፀሓይ ያበራዋል።

7. በእግዚአብሔር ፊት ጸጥ በል፤በትዕግሥትም ተጠባበቀው፤መንገዱ በተቃናለት፣ክፋትንም በሚሸርብ ሰው ልብህ አይሸበር።

8. ከንዴት ተቈጠብ፤ ቍጣንም ተወው፤ወደ እኵይ ተግባር እንዳይመራህ አትከፋ።

9. ክፉ ሰዎች ይጠፋሉና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን ምድርን ይወርሳሉ።

10. ለአፍታ እንጂ፣ ክፉ ሰው አይዘልቅም፤ስፍራውንም ብታስስ አታገኘውም።

11. ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፤በታላቅ ሰላምም ሐሤት ያደርጋሉ።

12. ክፉዎች በጻድቃን ላይ ያሤራሉ፤ጥርሳቸውንም ያፋጩባቸዋል።

13. እግዚአብሔር ግን ይሥቅባቸዋል፤ቀናቸው እንደ ደረሰ ያውቃልና።

14. ድኾችንና ችግረኞችን ለመጣል፣አካሄዳቸው ቀና የሆነውንም ለመግደል፣ክፉዎች ሰይፋቸውን መዘዙ፤ቀስታቸውንም ገተሩ።

15. ሰይፋቸው የገዛ ልባቸውን ይወጋል፤ቀስታቸውም ይሰበራል።

16. የጻድቅ ጥቂት ሀብት፣ከክፉዎች ብዙ ጥሪት ይበልጣል።

17. የክፉዎች ክንድ ይሰበራልና፤ጻድቃንን ግን እግዚአብሔር ደግፎ ይይዛቸዋል።

18. እግዚአብሔር የንጹሐንን የሕይወት ዘመን ያውቃል፤ርስታቸውም ለዘላለም ይኖራል።

19. በክፉ ጊዜ ዐንገት አይደፉም፤በራብ ዘመንም ይጠግባሉ።

20. ክፉዎች ግን ይጠፋሉ፤ የእግዚአብሔር ጠላቶች እንደ መስክ ውበት ይሆናሉ፤ይጠፋሉ፤ እንደ ጢስም ተነው ይጠፋሉ።

21. ኀጢአተኛ ይበደራል፤ መልሶም አይከፍልም፤ጻድቅ ግን ይቸራል።

22. እግዚአብሔር የባረካቸው ምድርን ይወርሳሉ፤እርሱ የሚረግማቸው ግን ይጠፋሉ።

23. የሰው አካሄድ በእግዚአብሔር ይጸናል፤በመንገዱ ደስ ይለዋል።

24. ቢሰናከልም አይወድቅም፤ እግዚአብሔር በእጁ ደግፎ ይይዘዋልና።

25. ጐልማሳ ነበርሁ፤ አሁን አርጅቻለሁ፤ነገር ግን ጻድቅ ሲጣል፣ዘሩም እንጀራ ሲለምን አላየሁም።

26. ሁል ጊዜ ቸር ነው፤ ያበድራልም፤ልጆቹም የተባረኩ ይሆናሉ።

27. ከክፉ ራቅ፤ መልካሙንም አድርግ፤ለዘላለምም ትኖራለህ።

28. እግዚአብሔር ፍትሕን ይወዳልና፤ታማኞቹንም አይጥልም፤ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል፤የኀጢአተኛው ዘር ግን ይጠፋል።

29. ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፤በእርሷም ለዘላለም ይኖራሉ።

30. የጻድቅ አፍ ጥበብን ይናገራል፤አንደበቱም ፍትሐዊ ነገር ያወራል።

31. የአምላኩ ሕግ በልቡ አለ፤አካሄዱም አይወላገድም።

32. ክፉዎች ጻድቁን ይከታተሉታል፤ሊገድሉትም ይሻሉ።

33. እግዚአብሔር ግን በእጃቸው አይጥለውም፤ፍርድ ፊት ሲቀርብም አሳልፎ አይሰጠውም።

34. እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፤መንገዱንም ጠብቅ፤ምድሪቱን ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤ክፉዎችም ሲጠፉ ታያለህ።

35. ክፉና ጨካኙን ሰው፣እንደ ሊባኖስ ዝግባ ለምልሞ አየሁት፤

36. ዳግመኛ በዚያ ሳልፍ፣ እነሆ፣ በቦታው አልነበረም፤ብፈልገውም አልተገኘም።

37. ንጹሐንን ልብ በል፤ ቅኑንም አስተውል፤የሰላም ሰው ተስፋ አለውና።

38. ኀጢአተኞች ግን በአንድነት ይጠፋሉ፤የክፉዎችም ዘር ይወገዳል።

39. የጻድቃን ድነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፤በመከራ ጊዜም መጠጊያቸው እርሱ ነው።

40. እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፤ይታደጋቸዋልም፤ከክፉዎች እጅ ነጥቆ ያወጣቸዋል፤እርሱን መጠጊያ አድርገዋልና ያድናቸዋል።