ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 39:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እኔ፣ “በአንደበቴ እንዳልበድል፣መንገዴን እጠብቃለሁ፤ክፉዎችም በእኔ ዘንድ እስካሉ ድረስ፣ልጓም በአፌ አስገባለሁ” አልሁ።

2. እንደ ዲዳ ዝም አልሁ፤ለበጎ ነገር እንኳ አፌን ዘጋሁ፤ሆኖም ጭንቀቴ ባሰ።

3. ልቤ በውስጤ ጋለ፤በማሰላስልበትም ጊዜ እሳቱ ነደደ፤ከዚያም በአንደበቴ እንዲህ ተናገርሁ፤

4. “እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።

5. እነሆ፤ ዘመኔን በስንዝር ለክተህ አስቀመጥህ፤ዕድሜዬም በፊትህ እንደ ኢምንት ነው፤በእርግጥ የሰው ሁሉ ሕይወት ተን ነው። ሴላ

6. ሰው የጥላ ውልብታ ነው፤በከንቱም ይታወካል፤ለማን እንደሚሆን ሳያውቅ ሀብት ንብረት ያከማቻል።

7. “ጌታ ሆይ፤ አሁንስ ወደ ማን ልመልከት?ተስፋዬ በአንተ ላይ ነው።

8. ከኀጢአቴ ሁሉ አድነኝ፤የሰነፎች መሣለቂያ አታድርገኝ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 39