ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 44 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ብሔራዊ ሰቆቃ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች ትምህርት።

1. አምላክ ሆይ፤ በጆሮአችን ሰምተናል፤አባቶቻችን በቀድሞ ዘመን፣እነርሱ በነበሩበት ዘመን፣ያደረግኸውን ነግረውናል።

2. ሕዝቦችን በእጅህ አሳደህ አወጣሃቸው፤አባቶቻችንን ግን ተከልሃቸው፤ሕዝቦችን አደቀቅህ፤አባቶቻችንን ግን ነጻ አወጣሃቸው።

3. ምድሪቱን የወረሱት በሰይፋቸው አልነበረም፤ድልንም የተጐናጸፉት በክንዳቸው አይደለም፤አንተ ወደሃቸዋልና ቀኝ እጅህ፣ክንድህና የፊትህ ብርሃን ይህን አደረገ።

4. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ንጉሤ ነህ፤ያዕቆብም ድል እንዲያደርግ የወሰንህ አንተ ነህ።

5. በአንተ ጠላቶቻችን በመጡበት እንዲመለሱ እናደርጋለን፤በስምህም ባላጋራዎቻችንን ከእግራችን በታች እንረግጣለን።

6. በቀስቴ አልተማመንም፤ሰይፌም አያስጥለኝም።

7. አንተ ግን በጠላቶቻችን ላይ ድልን ትሰጠናለህ፤ባላንጣዎቻችንንም ታሳፍራለህ።

8. ዘወትር በእግዚአብሔር እንመካለን፤ስምህንም ለዘላለም እንወድሳለን። ሴላ

9. አሁን ግን እነሆ ትተኸናል፤ አሳፍረኸናልም፤ከሰራዊታችንም ጋር አትወጣም።

10. ከጠላት ፊት እንድናፈገፍግ አደረግኸን፤ባላንጣዎቻችንም ዘረፉን።

11. እንደሚታረዱ በጎች አደረግኸን፤በሕዝቦችም መካከል በተንኸን።

12. ሕዝብህን በርካሽ ዋጋ ሸጥኸው፤ከሽያጩም ያገኘኸው ትርፍ የለም።

13. ለጎረቤቶቻችን ስድብ፣በዙሪያችን ላሉትም መሣቂያና መዘበቻ አደረግኸን።

14. በሕዝቦች ዘንድ መተረቻ፣በሰዎች መካከል በንቀት ራስ መነቅነቂያ አደረግኸን።

15. ውርደቴ ቀኑን ሙሉ በፊቴ ነው፤ፊቴም ዕፍረትን ተከናንቦአል።

16. ይህም ከሚዘልፍና ከሚያላግጥ ሰው ድምፅ የተነሣ፣ከጠላትና ከተበቃይ ሁኔታ የተነሣ ነው።

17. አንተን ሳንረሳ፣ለኪዳንህም ታማኝነታችንን ሳናጓድል፣ይህ ሁሉ ደረሰብን።

18. ልባችን ወደ ኋላ አላለም፤እግራችንም ከመንገድህ አልወጣም።

19. አንተ ግን ተኵላዎች በሚውሉበት ቦታ ሰባብረህ ጣልኸን፤በሞት ጥላም ሸፈንኸን።

20. የአምላካችንን ስም ረስተን፣እጃችንንም ወደ ባዕድ አምላክ ዘርግተን ቢሆን ኖሮ፣

21. እግዚአብሔር ይህን ማወቅ ይሳነዋልን?እርሱ ልብ የሰወረውን የሚረዳ ነውና።

22. ይሁን እንጂ ቀኑን ሙሉ ስለ አንተ ሞትን እንጋፈጣለን፤እንደሚታረዱ በጎችም ተቈጥረናል።

23. ጌታ ሆይ፤ ንቃ! ለምንስ ትተኛለህ?ተነሥ፤ ለዘላለምም አትጣለን።

24. ፊትህን ለምን ትሰውራለህ?መከራችንንና መጠቃታችንን ለምን ትረሳለህ?

25. ነፍሳችን ዐፈር ውስጥ ሰጥማለች፤ሆዳችንም ከምድር ጋር ተጣብቆአል።

26. ተነሥና እርዳን!ስለ ምሕረትህ ስትል ተቤዠን።