ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 48:2-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. የምድር ሁሉ ደስታ የሆነው፣በሰሜን በኩል በርቀት የሚታየው፣በከፍታ ላይ አምሮ የደመቀው የጽዮን ተራራ፣የታላቁ ንጉሥ ከተማ ነው።

3. እግዚአብሔር በአዳራሾቿ ውስጥ ሆኖ፤ብርቱ ምሽግ እንደሆናት አስመስክሮአል።

4. እነሆ፤ ነገሥታት ተባብረው መጡ፤አንድ ላይ ሆነውም ገሠገሡ።

5. አይተውም ተደነቁ፤ደንግጠውም ፈረጠጡ።

6. ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣በዚያ ብርክ ያዛቸው።

7. የምሥራቅ ነፋስ የተርሴስን መርከብ እንደሚሰባብር፣አንተ አብረከረክሃቸው።

8. እንደ ሰማን፣በሰራዊት አምላክ ከተማ፣በአምላካችን ከተማ፣እንዲሁ አየን፤እግዚአብሔር ለዘላለም ያጸናታል። ሴላ

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 48