ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 49 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የሀብት ከንቱነት

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1. እናንተ ሕዝቦች ሁላችሁ፤ ይህን ስሙ፤በዓለም የምትኖሩ ሁሉ፤ ይህን አድምጡ።

2. ዝቅተኞችና ከፍተኞች፤ባለጠጎችና ድኾች ይህን በአንድነት ስሙ።

3. አፌ የጥበብን ቃል ይናገራል፤የልቤም ሐሳብ ማስተዋልን ይሰጣል።

4. ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ፤እንቆቅልሼንም በበገና እፈታለሁ።

5. የአጭበርባሪዎች ክፋት በከበበኝ ጊዜ፣በክፉ ቀን ለምን እፈራለሁ?

6. በሀብታቸው የሚመኩትን፣በብልጽግናቸውም የሚታመኑትን ለምን እፈራለሁ?

7. የሌላውን ሕይወት መቤዠት የሚችል ሰው፣ወይም ለእግዚአብሔር ወጆ የሚከፍልለት ማንም የለም።

8. የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤

9. በዚህም ዘላለም ይኖራል፣መበስበስንም አያይም።

10. ጠቢባን ሟች መሆናቸው የሚታይ ነው፤ቂልና ሞኝም በአንድነት ይጠፋሉ፤ጥሪታቸውንም ለሌላው ጥለው ይሄዳሉ።

11. መሬቶችን በስማቸው ቢሰይሙም፣መቃብራቸው የዘላለም ቤታቸው፣ከትውልድ እስከ ትውልድም መኖሪያቸው ይሆናል።

12. ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።

13. ይህ የተላላዎች ዕድል ፈንታ፣የእነርሱንም አባባል ተቀብለው ለሚከተሏቸው፣መጨረሻ ግብ ነው። ሴላ

14. እንደ በጎች ለሲኦል የተዳረጉ ናቸው፤ሞትም እረኛቸው ይሆናል፤ቅኖች በማለዳ ይገዟቸዋል፤አካላቸው ከክብር ቤታቸው ርቆ፣በሲኦል ይፈራርሳል።

15. እግዚአብሔር ግን ነፍሴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል፤በርግጥም በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለኝ። ሴላ

16. ሰው ባለጠጋ ሲሆን፣የቤቱም ክብር ሲበዛለት አትፍራ፤

17. በሚሞትበትም ጊዜ ይዞት የሚሄደው አንዳች የለምና፤ክብሩም አብሮት አይወርድም።

18. በሕይወት ሳለ ራሱን እንደ ተባረከ ቢቈጥርም፣ሰዎች በበለጸግህ ጊዜ ቢያወድሱህም፣

19. ብርሃን ከቶ ወደማያዩት፣ወደ አባቶች ማኅበር ይቀላቀላል።

20. ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።