ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 50:3-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. አምላካችን ይመጣል፤ ዝምም አይልም፤የሚባላ እሳት በፊቱ፣የሚያስፈራ ዐውሎ ነፋስም በዙሪያው አለ።

4. በሕዝቡ ይፈርድ ዘንድ፣በላይ ያለውን ሰማይንና ምድርን እንዲህ ብሎ ይጠራል፤

5. “በመሥዋዕት ከእኔ ጋር ኪዳን የገቡትን፣ቅዱሳኔን ወደ እኔ ሰብስቧቸው።”

6. ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፤እግዚአብሔር ራሱ ፈራጅ ነውና። ሴላ

7. “ሕዝቤ ሆይ፤ ስማኝ፤ ልንገርህ፤እስራኤል ሆይ፤ በአንተ ላይ ልመስክር፤አምላክህ እኔ እግዚአብሔር ነኝ።

8. ስለ መሥዋዕትህ አልነቀፍሁህም፤የሚቃጠል መሥዋዕትህማ ሁል ጊዜ በፊቴ ነው።

9. እኔ ግን ኮርማህን ከበረት፣ፍየሎችህንም ከጒረኖ የምፈልግ አይደለሁም፤

10. የዱር አራዊት ሁሉ፣በሺ ተራራዎች ላይ ያለውም እንስሳ የእኔ ነውና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 50