ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 59:9-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ብርታቴ ሆይ፤ አንተን እጠብቃለሁ፤አምላክ ሆይ፤ አንተ መጠጊያዬ ነህና።

10. እግዚአብሔር በምሕረቱ ይገናኘኛል፤አምላኬ የጠላቶቼን ውድቀት ያሳየኛል።

11. ጋሻችን ጌታ ሆይ፤ አትግደላቸው፤አለበለዚያ ሕዝቤ ይረሳል፤በኀይልህ አንከራታቸው፤ዝቅ ዝቅም አድርጋቸው።

12. ከአፋቸው ስለሚወጣው ኀጢአት፣ከከንፈራቸውም ስለሚሰነዘረው ቃል፣በትዕቢታቸው ይያዙ።ስለ ተናገሩት መርገምና ውሸት፣

13. በቊጣ አጥፋቸው፤ፈጽመህም አስወግዳቸው፤በዚህም እግዚአብሔር የያዕቆብ ገዥ መሆኑ፣እስከ ምድር ዳርቻ ይታወቃል። ሴላ

14. እንደ ውሻ እያላዘኑ፣በምሽት ተመልሰው ይመጣሉ፤በከተማዪቱም ዙሪያ ይራወጣሉ።

15. ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ።ካልጠገቡም ያላዝናሉ።

16. እኔ ግን ስለ ኀይልህ እዘምራለሁ፤በማለዳም ስለ ምሕረትህ እዘምራለሁ፤አንተ መጠጊያዬ፣በመከራም ቀን ዐምባዬ ነህና።

17. ብርታቴ ሆይ፤ ውዳሴ አቀርብልሃለሁ፤እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ መጠጊያዬ፣የምትወደኝም አምላኬ ነህና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 59