ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 66:1-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል ይበል!

2. ለስሙ ክብር ዘምሩ፤ውዳሴውንም አድምቁ

3. እግዚአብሔርን እንዲህ በሉት፤ “ሥራህ እንዴት ግሩም ነው!ጠላቶችህ ከኀይልህ ታላቅነት የተነሣ፣በፊትህ ይርዳሉ።

4. ምድር ሁሉ ይሰግድልሃል፤በዝማሬ ያመሰግኑሃል፤ለስምህም ይዘምራሉ። ሴላ

5. ኑና፣ እግዚአብሔር ያደረገውን እዩበሰዎች መካከል ሥራው አስፈሪ ነው!

6. ባሕሩን የብስ አደረገው፤ወንዙን በእግር ተሻገሩ፤ኑ፣ በእርሱ ደስ ይበለን።

7. በኀይሉ ለዘላለም ይገዛል፤ዐይኖቹ ሕዝቦችን ይመለከታሉ፤እንግዲህ ዐመፀኞች ቀና ቀና አይበሉ። ሴላ

8. ሕዝቦች ሆይ፤ አምላካችንን ባርኩ፤የምስጋናውንም ድምፅ አሰሙ።

9. እኛን በሕይወት የሚያኖረን፣እግራችንንም ከመንሸራተት የሚጠብቅ እርሱ ነው።

10. አምላክ ሆይ፤ አንተ ፈተንኸን፤እንደ ብርም አነጠርኸን።

11. ወደ ወጥመድ አገባኸን፤በጀርባችንም ሸክም ጫንህብን።

12. ሰዎች በራሳችን ላይ እንዲፈነጩ አደረግህ፤በእሳትና በውሃ መካከል አለፍን፤የኋላ ኋላ ግን ወደ በረከት አመጣኸን።

13. የሚቃጠል መሥዋዕት ይዤ ወደ መቅደስህ እገባለሁ፤ስእለቴንም ለአንተ እፈጽማለሁ፤

14. በመከራ ጊዜ ከአፌ የወጣ፣በከንፈሬም የተናገርሁት ስእለት ነው።

15. ፍሪዳዎችን የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጌ፣አውራ በጎችንም የሚጤስ ቍርባን አድርጌ አቀርብልሃለሁ፤ኰርማዎችንና ፍየሎችንም እሠዋልሃለሁ። ሴላ

16. እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሁሉ፤ ኑና ስሙ፤ለነፍሴ ያደረገላትን ልንገራችሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 66