ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 73:19-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. እንዴት ፈጥነው በቅጽበት ጠፉ!በድንጋጤ ፈጽመው ወደሙ።

20. ሰው ከሕልሙ ሲነቃ እንደሚሆነው፣ጌታ ሆይ፤ አንተም በምትነሣበት ጊዜ፣እንደ ቅዠት ከንቱ ታደርጋቸዋለህ።

21. ነፍሴ በተማረረች ጊዜ፣ልቤም በተቀሠፈ ጊዜ፣

22. ስሜት የሌለውና አላዋቂ ሆንሁ፤በፊትህም እንደ እንስሳ ሆንሁ።

23. ይህም ሆኖ ዘወትር ከአንተ ጋር ነኝ፤አንተም ቀኝ እጄን ይዘኸኛል።

24. በምክርህ መራኸኝ፤ኋላም ወደ ክብር ታስገባኛለህ።

25. በሰማይ ከአንተ በቀር ማን አለኝ?በምድርም ከአንተ ሌላ የምሻው የለኝም።

26. ሥጋዬና ልቤ ሊደክሙ ይችላሉ፤እግዚአብሔር ግን የልቤ ብርታት፣የዘላለም ዕድል ፈንታዬ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 73