ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 73:20-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. ሰው ከሕልሙ ሲነቃ እንደሚሆነው፣ጌታ ሆይ፤ አንተም በምትነሣበት ጊዜ፣እንደ ቅዠት ከንቱ ታደርጋቸዋለህ።

21. ነፍሴ በተማረረች ጊዜ፣ልቤም በተቀሠፈ ጊዜ፣

22. ስሜት የሌለውና አላዋቂ ሆንሁ፤በፊትህም እንደ እንስሳ ሆንሁ።

23. ይህም ሆኖ ዘወትር ከአንተ ጋር ነኝ፤አንተም ቀኝ እጄን ይዘኸኛል።

24. በምክርህ መራኸኝ፤ኋላም ወደ ክብር ታስገባኛለህ።

25. በሰማይ ከአንተ በቀር ማን አለኝ?በምድርም ከአንተ ሌላ የምሻው የለኝም።

26. ሥጋዬና ልቤ ሊደክሙ ይችላሉ፤እግዚአብሔር ግን የልቤ ብርታት፣የዘላለም ዕድል ፈንታዬ ነው።

27. እነሆ፤ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉና፤አንተ ታማኞች ያልሆኑልህን ሁሉ ታጠፋቸዋለህ።

28. ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ጌታ እግዚአብሔርን መጠጊያዬ አድርጌዋለሁ፤ስለ ሥራህም ሁሉ እናገር ዘንድ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 73