ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 89:24-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

24. ታማኝነቴና ምሕረቴ ከእርሱጋር ይሆናል፤በስሜም ቀንዱ ከፍ ከፍ ይላል።

25. እጁን በባሕር ላይ፣ቀኝ እጁንም በወንዞች ላይ አኖራለሁ።

26. እርሱም፣ ‘አንተ አባቴ ነህ፤አምላኬና መዳኛ ዐለቴም ነህ’ ብሎ ይጠራኛል።

27. እኔም ደግሞ በኵሬ አደርገዋለሁ፤ከምድር ነገሥታትም በላይ ከፍ ይላል።

28. ምሕረቴንም ለዘላለም ለእርሱ እጠብቃለሁ፤ከእርሱ ጋር የገባሁት ኪዳንም ጸንቶ ይኖራል።

29. የዘር ሐረጉን ለዘላለም፣ዙፋኑንም በሰማያት ዕድሜ ልክ አጸናለሁ።

30. “ልጆቹ ሕጌን ቢተዉ፣ደንቤን ባይጠብቁ፣

31. ሥርዐቴን ቢጥሱ፣ትእዛዜንም ባያከብሩ፣

32. ኀጢአታቸውን በበትር፣በደላቸውን በጅራፍ እቀጣለሁ።

33. ምሕረቴን ግን ከእርሱ አላርቅም፤ታማኝነቴንም አላጓድልበትም።

34. ኪዳኔን አላፈርስም፤ከአፌ የወጣውንም አላጥፍም።

35. አንድ ጊዜ በቅድስናዬ ምያለሁና፣ዳዊትን አልዋሸውም።

36. የዘር ሐረጉ ለዘላለም፣ዙፋኑም በፊቴ እንደ ፀሓይ ጸንቶ ይኖራል፤

37. በሰማይ ታማኝ ምስክር ሆና እንደምትኖረው፣እንደ ጨረቃ እርሱ ለዘላለም ይመሠረታል።” ሴላ

38. አሁን ግን ናቅኸው፤ ጣልኸውም፤የቀባኸውንም እጅግ ተቈጣኸው።

39. ከባሪያህ ጋር የገባኸውን ኪዳን አፈረስህ፤የክብር ዘውዱን ትቢያ ላይ ጥለህ አቃለልኸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 89