ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 89:31-40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

31. ሥርዐቴን ቢጥሱ፣ትእዛዜንም ባያከብሩ፣

32. ኀጢአታቸውን በበትር፣በደላቸውን በጅራፍ እቀጣለሁ።

33. ምሕረቴን ግን ከእርሱ አላርቅም፤ታማኝነቴንም አላጓድልበትም።

34. ኪዳኔን አላፈርስም፤ከአፌ የወጣውንም አላጥፍም።

35. አንድ ጊዜ በቅድስናዬ ምያለሁና፣ዳዊትን አልዋሸውም።

36. የዘር ሐረጉ ለዘላለም፣ዙፋኑም በፊቴ እንደ ፀሓይ ጸንቶ ይኖራል፤

37. በሰማይ ታማኝ ምስክር ሆና እንደምትኖረው፣እንደ ጨረቃ እርሱ ለዘላለም ይመሠረታል።” ሴላ

38. አሁን ግን ናቅኸው፤ ጣልኸውም፤የቀባኸውንም እጅግ ተቈጣኸው።

39. ከባሪያህ ጋር የገባኸውን ኪዳን አፈረስህ፤የክብር ዘውዱን ትቢያ ላይ ጥለህ አቃለልኸው።

40. ቅጥሩን ሁሉ አፈራረስህ፤ምሽጉንም ደመሰስህ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 89