ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 9:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ።

2. በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ።

3. ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ፣ተሰነካክለው ከፊትህ ይጠፋሉ፤

4. ፍርዴም ጒዳዬም በአንተ እጅ ናቸውና፤ቅን ፍርድ እየሰጠህ በዙፋንህ ላይ ተቀምጠሃል።

5. ሕዝቦችን ገሠጽህ፤ ክፉዎችንም አጠፋህ፤ስማቸውንም እስከ ወዲያኛው ደመሰስህ።

6. ጠላቶች ለዘላለም ጠፉ፤ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው፤መታሰቢያቸውም ተደምስሶአል።

7. እግዚአብሔር ግን ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ነው፤መንበሩንም ለፍርድ አጽንቶአል።

8. ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል፤ሕዝቦችንም በፍትሕ ይገዛል።

9. እግዚአብሔር ለተጨቈኑት ዐምባ ነው፤በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል።

10. ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና።

11. በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ሥራውንም በሕዝቦች መካከል በግልጽ አውሩ፤

12. ደም ተበቃዩ ዐስቦአቸዋልና፤የጭቍኖችንም ጩኸት አልዘነጋም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 9