2. አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።
3. ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?
4. የእብሪት ቃላት ያዥጐደጒዳሉ፤ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጒራ ይነዛሉ።
5. እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤ርስትህንም አስጨነቁ።
6. መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤የድኻ አደጉንም ነፍስ አጠፉ።
7. እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።
8. እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?
9. ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?