ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 6:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር የሚለውን ስሙ፤“ተነሡ፤ ጒዳያችሁን በተራሮችም፤ፊት አቅርቡ፤ኰረብቶች እናንተ የምትሉትን ይስሙ፤

2. ተራሮች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ክስ አድምጡ፤እናንት የምድር ጽኑ መሠረቶችም፤ ስሙ፤ እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ክርክር አለውና፤ከእስራኤልም ጋር ይፋረዳል።

3. “ሕዝቤ ሆይ፤ ምን አድርጌሃለሁ?ሸክም የሆንሁብህስ እንዴት ነው?እስቲ መልስልኝ!

4. ከግብፅ አወጣሁህ፤ከባርነት ምድርም ተቤዠሁህ፤እንዲመሩህ ሙሴን፣አሮንንና ማርያምን ላክሁልህ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 6