ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 1:27-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. መዓት እንደ ማዕበል ሲያናውጣችሁ፣መከራም እንደ ዐውሎ ነፋስ ሲጠራርጋችሁ፣ሥቃይና ችግር ሲያጥለቀልቃችሁ አፌዝባችኋለሁ።

28. “በዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፤ እኔ ግን አልመልስላቸውም፤አጥብቀው ይፈልጉኛል፤ ነገር ግን አያገኙኝም።

29. ዕውቀትን ስለ ጠሉ፣ እግዚአብሔርንም መፍራት ስላልመረጡ፣

30. ምክሬን ለመቀበል ስላልፈለጉ፣ዘለፋዬን ስለናቁ፣

31. የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፤የዕቅዳቸውንም ውጤት ይጠግባሉ።

32. ብስለት የሌላቸውን ስድነታቸው ይገድላቸዋል፤ተላሎችንም ቸልተኝነታቸው ያጠፋቸዋል፤

33. የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ምሳሌ 1