ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሰቆቃወ 3:28-40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

28. ብቻውን ዝም ብሎ ይቀመጥ፤ እግዚአብሔር አሸክሞታልና።

29. ፊቱን በዐቧራ ውስጥ ይቅበር፤ተስፋ ሊኖር ይችላልና።

30. ጒንጩን ለሚመታው ሰው ይስጥ፤ውርደትንም ይጥገብ።

31. እግዚአብሔር ሰውን፣ለዘላለም አይጥልምና፤

32. መከራን ቢያመጣ እንኳ ይራራል፤ታላቅ ፍቅሩ አይለወጥምና

33. ሆን ብሎ ችግርን፣ወይም መከራን በሰው ልጆች ላይ አያመጣምና።

34. የምድሪቱ እስረኞች ሁሉ፣በእግር ሲረገጡ፣

35. በልዑል ፊት፣ሰው መብቱ ሲነፈገው፣

36. ሰው ፍትሕ ሲጓደልበት፣ጌታ እንዲህ ዐይነቱን ነገር አያይምን?

37. እግዚአብሔር ካላዘዘ በቀር፤ተናግሮ መፈጸም የሚችል ማን ነው?

38. ክፉም ሆነ መልካም ነገር፣ከልዑል አፍ የሚወጣ አይደለምን?

39. ታዲያ ሕያው ሰው በኀጢአቱ ሲቀጣ፣ስለ ምን ያጒረመርማል?

40. መንገዳችንን እንመርምር፤ እንፈትን፤ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሰቆቃወ 3