ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 1:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2. እርሱም እንዲህ አለ፤“እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጒዳል፤የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል፤የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጎአል።”

3. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቊጣዬን አልመልስም፤የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣ ገለዓድንአሂዳለችና፤

4. የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣ በአዛሄልቤት ላይ እሳት እሰዳለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 1