ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 7:14-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. አሞጽም ለአሜስያስ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እኔ እረኛና የባሉጥ ፍሬ ለቃሚ ነኝ እንጂ ነቢይ ወይም የነቢይ ልጅ አይደለሁም፤

15. እግዚአብሔር ግን የበግ መንጋ ከምጠብቅበት ቦታ ወስዶ፣ ‘ሂድና ለሕዝቤ ለእስራኤል ትንቢት ተናገር’ አለኝ፤

16. እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ።አንተ፣ “ ‘በእስራኤል ላይ ትንቢት አትናገር፤በይስሐቅም ቤት ላይ አትስበክ’ ትላለህ።

17. “ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤”‘ሚስትህ በከተማዪቱ ውስጥ ጋለሞታ ትሆናለች፤ወንዶችና ሴቶች ልጆችህም በሰይፍ ይወድቃሉ፤ምድርህም እየተለካ ይከፋፈላል፤አንተ ራስህ በረከሰ ምድር ትሞታለህ፤እስራኤልም ከትውልድ አገሩ፣ተማርኮ ይሄዳል።’ ”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 7