26. “ ‘ይህን ቀድሞ እንደ ወሰንሁት፣ጥንትም እንዳቀድሁት፣አልሰማህምን?አሁን ደግሞ እንዲፈጸም አደረግሁት፤አንተም የተመሸጉትን ከተሞች የድንጋይክምር አደረግሃቸው።
27. የሕዝቦቻቸው ኀይል ተሟጦአል፤ደንግጠዋል፤ ተዋርደዋልም፤በሜዳ እንዳሉ ዕፀዋት፣እንደ ለጋ ቡቃያ፣በሰገነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፣በእንጭጩ ዋግ እንደ መታው ሆነዋል።
28. “ ‘እኔ ግን የት እንዳለህ፣መምጣት መሄድህ ምን ጊዜ እንደሆነ፣በእኔም ላይ እንዴት በቍጣ እንደም ትነሣሣ ዐውቃለሁ።
29. በእኔ ላይ በቍጣ ስለ ተነሣሣህ፣እብሪትህም ወደ ጆሮዬ ስለ ደረሰ፣በአፍንጫህ ስናጌን፣በአፍህ ልጓሜን አገባለሁ፤በመጣህበትም መንገድ እንድትመለስአደርግሃለሁ።’