ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 37:26-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. “ ‘ይህን ቀድሞ እንደ ወሰንሁት፣ጥንትም እንዳቀድሁት፣አልሰማህምን?አሁን ደግሞ እንዲፈጸም አደረግሁት፤አንተም የተመሸጉትን ከተሞች የድንጋይክምር አደረግሃቸው።

27. የሕዝቦቻቸው ኀይል ተሟጦአል፤ደንግጠዋል፤ ተዋርደዋልም፤በሜዳ እንዳሉ ዕፀዋት፣እንደ ለጋ ቡቃያ፣በሰገነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፣በእንጭጩ ዋግ እንደ መታው ሆነዋል።

28. “ ‘እኔ ግን የት እንዳለህ፣መምጣት መሄድህ ምን ጊዜ እንደሆነ፣በእኔም ላይ እንዴት በቍጣ እንደም ትነሣሣ ዐውቃለሁ።

29. በእኔ ላይ በቍጣ ስለ ተነሣሣህ፣እብሪትህም ወደ ጆሮዬ ስለ ደረሰ፣በአፍንጫህ ስናጌን፣በአፍህ ልጓሜን አገባለሁ፤በመጣህበትም መንገድ እንድትመለስአደርግሃለሁ።’

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 37