ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 19:20-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. ቈዳና ዐጥንት ብቻ ሆኜ ቀረሁ፤ድድ ብቻ ቀርቶልኝ አመለጥሁ።

21. “ወዳጆቼ ሆይ፤ ራሩልኝ፤የእግዚአብሔር እጅ መታኛለችና ዕዘኑልኝ።

22. እግዚአብሔር እንዳሳደደኝ ለምን ታሳድዱኛላችሁ?አሁንም ሥጋዬ አልበቃችሁምን?

23. “ምነው ቃሌ በተጻፈ ኖሮ!በመጽሐፍም በታተመ!

24. ምነው በብረትና በእርሳስ በተጻፈ ኖሮ!በዐለትም ላይ በተቀረጸ!

25. የሚቤዠኝ ሕያው እንደሆነ፣በመጨረሻም በምድር ላይ እንደሚቆም ዐውቃለሁ።

26. ቈዳዬ ቢጠፋም፣ከሥጋዬ ብለይም፣ እግዚአብሔርን አየዋለሁ፤

27. ሌላ ሳይሆን እኔው በገዛ ዐይኔ፣እኔ ራሴ አየዋለሁ፤ልቤ በውስጤ ምንኛ በጉጉት ዛለ!

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 19