ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 41:27-34 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. እርሱ ብረትን እንደ አገዳ፣ናስንም እንደ ነቀዘ ዕንጨት ይቈጥራል።

28. ቀስት አያባርረውም፤የወንጭፍ ድንጋይም ለእርሱ እንደ ገለባ ነው።

29. ቈመጥ በእርሱ ፊት እንደ ገለባ ነው፤ጦር ሲሰበቅ ይሥቃል።

30. የሆዱ ሥር እንደ ሸካራ ገል ነው፤እንደ መውቂያ መሣሪያም በጭቃ ላይ ምልክት ጥሎ ያልፋል።

31. እንደሚፈላ ምንቸት ጥልቁን ያናውጠዋል፤ባሕሩንም እንደ ሽቶ ብልቃጥ ያደርገዋል።

32. ያለፈበትን መንገድ ብሩህ ያደርጋል፤ቀላዩንም ሽበት ያወጣ ያስመስለዋል።

33. ያለ ፍርሀት የተፈጠረ፣እንደ እርሱ ያለ በምድር ላይ የለም።

34. ከፍ ያሉትን ሁሉ በንቀት ይመለከታል፤በትዕቢተኞችም ሁሉ ላይ ንጉሥ ነው።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 41