ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 22:18-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤“ ‘ዋይ ወንድሜ! ዋይ፣ እኅቴን!’ብለው አያለቅሱለትም።‘ዋይ፣ ጌታዬን! ዋይ፣ ለግርማዊነቱ!’ብለውም አያለቅሱለትም።

19. አህያ እንደሚቀበር ይቀበራል፤ከኢየሩሳሌም በሮች ውጪ፤ተጐትቶ ይጣላል።

20. “ሊባኖስ ላይ ወጥተሽ ጩኺ፤ድምፅሽን በባሳን አሰሚ፤በዓባሪም ሆነሽ ጩኺ፤ወዳጆችሽ ሁሉ ወድመዋልና።

21. ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤ቃሌንም አልሰማሽም።

22. እረኞችሽ ሁሉ በነፋስ ይወሰዳሉ፤ወዳጆችሽም ተማርከው ይሄዳሉ፤ከክፋትሽም ሁሉ የተነሣ፣ታፍሪያለሽ፤ ትዋረጂያለሽም።

23. አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’ ውስጥ የምትኖሪ፣መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!

24. “በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 22