ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 48:22-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

22. በዲቦን፣ በናባውና በቤት ዲብላታይም ላይ፣

23. በቂርያታይም፣ በቤት ጋሙልና በቤትምዖን ላይ፣

24. በቂርዮትና በባሶራ ላይ፤በሩቅና በቅርብ፣ ባሉት በሞዓብ ከተሞች ሁሉ ላይ መጥቶአል።

25. የሞዓብ ቀንድ ተቈርጦአል፤እጁም ተሰባብሮአል፤”ይላል እግዚአብሔር።

26. “እግዚአብሔርን ንቆአልና፣ሞዓብን በመጠጥ አስክሩት።ሞዓብ በትፋቱ ላይ ይንከባለል፤ለመዘባበቻም ይሁን።

27. በእስራኤል ላይ ስታላግጥ አልነበረምን?ስለ እርሷ በተናገርህ ቍጥር፣እያቃለልሃት ራስህን የምትነቀንቀውስ፣ከሌቦች ጋር ስትሰርቅ ተይዛለችን?

28. እናንተ በሞዓብ የምትኖሩ ሆይ፤ከከተማ ወጥታችሁ በዐለት መካከል ኑሩ፤በገደል አፋፍ ላይ ጐጆዋን እንደምትሠራ፣እንደ ርግብ ሁኑ።

29. “ስለ ሞዓብ ትዕቢት፣ስለ እብሪቱና ስለ ኵራቱ፣ስለ ትምክሕቱና ስለ መጓደዱ፣ስለ ልቡም ማበጥ ሰምተናል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 48