ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 50:19-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. እስራኤልንም ወደ መሰማሪያው እመልሰዋለሁ፤በቀርሜሎስና በባሳን ላይ ይሰማራል፤በኤፍሬም ተራሮችና በገለዓድም ላይ፣እስኪጠግብ ይመገባል።

20. በእነዚያ ጊዜያት፣ በዚያ ዘመን፣”ይላል እግዚአብሔር፤“የእስራኤል በደል ይፈለጋል፤አንዳችም አይገኝም፤የይሁዳም ኀጢአት ይፈለጋል፤ከቶም የለም፤እንዲተርፉ ያደረግኋቸውን ትሩፋን እምራለሁና።

21. “የምራታይምን ምድር፣የፋቁድ ነዋሪዎችንም፣አሳዷቸው፤ ግደሏቸው፤ ፈጽማችሁም አጥፏቸው፤”ይላል እግዚአብሔር፤“ያዘዝኋችሁንም ሁሉ አድርጉ።

22. በምድሪቱ የጦርነት ውካታ፣የታላቅ ጥፋት ድምፅ ተሰማ።

23. የምድር ሁሉ መዶሻ፣እንዴት ተሰበረ! እንዴትስ ደቀቀ!በሕዝቦች መካከል፣ባቢሎን እንዴት ባድማ ሆነች!

24. ባቢሎን ሆይ፤ ወጥመድ ዘርግቼልሻለሁ፤አንቺም ሳታውቂ ተይዘሻል፤ እግዚአብሔርን ተገዳድረሻልና፣ተገኘሽ፤ ተያዝሽም።

25. እግዚአብሔር የመሣሪያ ግምጃ ቤቱን ከፍቶአል፤የቍጣውን የጦር ዕቃ አውጥቶአል፤የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በባቢሎናውያን ምድር ሥራ አለውና።

26. ከሩቅ መጥታችሁ በእርሷ ላይ ውጡ፤ጐተራዎቿን አፈራርሱ፤እንደ እህል ክምር ከምሯት፤ፈጽማችሁ አጥፏት፤ምኗም አይቅር።

27. ወይፈኖቿን ሁሉ ዕረዱ፤ወደ መታረጃም ይውረዱ!የሚቀጡበት ጊዜ፣ቀናቸው ደርሶአልና ወዮላቸው!

28. እግዚአብሔር አምላካችን የተበቀለውን፣ስለ ቤተ መቅደሱ የተበቀለውን በቀል፣ከባቢሎን የመጡ ኰብላዮችና ስደተኞች፣በጽዮን የሚናገሩትን ስሟቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 50