ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 51:36-41 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

36. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ እሟገትልሻለሁ፣በቀልሽንም እኔ እበቀልልሻለሁ፤ባሕሯን አደርቃለሁ፣የምንጮቿንም ውሃ።

37. ባቢሎን የፍርስራሽ ክምር፣የቀበሮዎች መፈንጫ፣የድንጋጤና የመሣለቂያ ምልክት ትሆናለች፤የሚኖርባትም አይገኝም።

38. ሕዝቦቿ ሁሉ እንደ ደቦል አንበሳ ያገሣሉ፤እንደ አንበሳ ግልገልም ያጒረመርማሉ።ጒሮሮአቸው በደረቀ ጊዜድግስ አዘጋጅላቸዋለሁ፤እንዲሰክሩም አደርጋቸውና፤”

39. በሣቅ እየፈነደቁ፣ለዘላለም ላይነቁ ይተኛሉ።”ይላል እግዚአብሔር።

40. “እንደ ጠቦት፣እንደ አውራ በግና እንደ ፍየል፣ወደ መታረድ አወርዳቸዋለሁ።

41. “ሼሻክ እንዴት ተማረከች!የምድር ሁሉ ትምክህትስ እንዴት ተያዘች!ባቢሎን በሕዝብ ሁሉ ዘንድ፣ምንኛ አስደንጋጭ ሆነች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 51