ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 6:15-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. ስለ ጸያፉ ተግባራቸው ዐፍረዋል እንዴ?ኧረ ጨርሶ ዕፍረት የላቸውም!ዕፍረት ምን እንደሆነ እንኳ አያውቁም፤ስለዚህ ከሚወድቁት ጋር ይወድቃሉ፤በምቀጣቸውም ጊዜ ይዋረዳሉ፤”ይላል እግዚአብሔር።

16. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“መንታ መንገድ ላይ ቁሙ፣ ተመልከቱም፤መልካሟን፣ የጥንቷን መንገድ ጠይቁ፤በእርሷም ላይ ሂዱ።ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ፤እናንተ ግን፣ ‘በእርሷ አንሄድም’ አላችሁ።

17. ጠባቂዎችን አቆምሁላችሁ፤‘የመለከትንም ድምፅ ስሙ’ አልኋችሁ፤እናንተ ግን፣ ‘አንሰማም’ አላችሁ።

18. እንግዲህ ሕዝቦች ሆይ ስሙ፤እናንተም ምስክሮች ምንእንደሚገጥማቸው አስተውሉ።

19. ምድር ሆይ፤ ስሚ፤ቃሌን ስላላደመጡ፣ሕጌንም ስለናቁ፣በዚህ ሕዝብ ላይ የሐሳባቸውን ውጤት፣ጥፋትን አመጣባቸዋለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 6