ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 8:10-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ስለዚህ ሚስቶቻቸውንም ለሌሎች ወንዶች እሰጣለሁ፤ዕርሻዎቻቸውንም ለባዕዳን እሰጣለሁ፤ከታናሹ እስከ ታላቁ ድረስ፣ሁሉም ተገቢ ላልሆነ ጥቅም ይስገበገባሉ፤ነቢያትና ካህናትም እንዲሁ፤ሁሉም ያጭበረብራሉ።

11. የሕዝቤን ቍስል ብርቱ እንዳይደለ በመቍጠር፣የተሟላ ፈውስ ሳይኖር እንዲሁ ያክማሉ፤ሰላም ሳይኖር፣“ሰላም፣ ሰላም” ይላሉ።

12. ርኵሰት ሲፈጽሙ ዐፍረው ነበርን?የለም! በጭራሽ አላፈሩም፤ኀፍረት ምን እንደሆነም አያውቁም።ስለዚህ ከወደቁት ጋር ይወድቃሉ፤በምቀጣቸው ጊዜ ይዋረዳሉ፤”ይላል እግዚአብሔር።

13. “ ‘ያመረቱትን ሁሉ እወስድባቸዋለሁ፤ይላል እግዚአብሔር፤በወይን ተክል ላይ የወይን ፍሬ አይኖርም፤በበለስ ዛፍ ላይ የበለስ ፍሬ አይገኝም፤ቅጠሎቻቸውም ይረግፋሉ።የሰጠኋቸው በሙሉ፣ከእነርሱ ይወሰድባቸዋል።’ ”

14. “ለምን እዚህ እንቀመጣለን?በአንድነት ተሰብሰቡ!ወደ ተመሸጉት ከተሞች እንሽሽ፤በዚያም እንጥፋ!በእርሱ ላይ ኀጢአትን ስላደረግን፣ እግዚአብሔር አምላካችን እንድንጠፋ አድርጎናል፤የተመረዘ ውሃ እንድንጠጣ ሰጥቶናል።

15. ሰላምን ተስፋ አደረግን፤መልካም ነገር ግን አልመጣም፤የፈውስ ጊዜን ተመኘን፤ነገር ግን ሽብር ብቻ ሆነብን።

16. የጠላት ፈረሶች ፉርፉርታ፣ከዳን ይሰማል፤በድንጒላ ፈረሶቻቸው ማሽካካት፣መላዋ ምድር ተንቀጠቀጠች።ምድሪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ፣ከተማዪቱንና በውስጧ የሚኖሩትን ሁሉ፣ሊውጡ መጡ።”

17. “እነሆ፤ በመካከላችሁ መርዘኛ እባቦችን፣የአስማተኛ ብልኀት የማይገታቸው እፉኝቶችን እሰዳለሁ፤እነርሱም ይነድፉአችኋል፤”ይላል እግዚአብሔር።

18. በሐዘኔ የምታጽናናኝ ሆይ፤ልቤ በውስጤ ዝላለች።

19. እንዲህ የሚለውን የሕዝቤን ጩኸት፣ከሩቅ ምድር ስማ፦ እግዚአብሔር በጽዮን የለምን?ንጉሥዋስ በዚያ አይኖርምን?”“በተቀረጹ ምስሎቻቸው፣እንዲሁም ከንቱ በሆኑ ባዕዳን ለምን አስቈጡኝ?”

20. “መከሩ ዐለፈ፤በጋው አበቃ፤እኛም አልዳንም።”

21. ሕዝቤ ሲቈስል፣እኔም ቈሰልሁ፤አለቀስሁ፤ ድንጋጤ ያዘኝ።

22. በገለዓድ የሚቀባ መድኀኒት የለምን?ወይስ በዚያ ሐኪም አልነበረምን?ለሕዝቤ ቍስል፣ለምን ፈውስ አልተገኘም?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 8