ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 9:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ስለ ታረዱት ወገኖቼ፣ቀንና ሌሊት አለቅስ ዘንድ፣ምነው፣ ራሴ የውሃ ምንጭ በሆነ!ምነው ዐይኖቼ የእንባ መጒረፊያ በሆኑልኝ!

2. ሕዝቤን ትቼ፣ ርቄ እንድሄድ፣በምድረ በዳ የእንግዶች ማደሪያ ማን በሰጠኝ!ሁሉም አመንዝሮች፣የአታላዮች መንጋ ሆነዋላ!

3. “ሐሰትን ለመናገር፣ምላሳቸውን እንደ ቀስት ገተሩ፤በእውነት ሳይሆን፣በሐሰት በምድሪቱ ገነኑ፤ከክፋት ወደ ክፋት ሄዱ፤እኔንም አላወቁኝም፤”ይላል እግዚአብሔር።

4. “እያንዳንዱ ወንድም አታላይ፣ባልንጀራም ሁሉ ሐሜተኛ ስለ ሆነ፣ወንድም ከወንድሙ፣ ይጠንቀቅ፣ባልንጀራም በጓደኛው አይታመን።

5. ባልንጀራ ባልንጀራውን ያታልላል፤እውነትን የሚናገር የለም፤ሐሰትን ይናገር ዘንድ ምላሳቸውን አሠልጥነዋል፤ኀጢአትንም በማድረግ ራሳቸውን አድክመዋል።

6. መኖሪያህ በሽንገላ መካከል ነው፤ከሽንገላቸውም የተነሣ ሊያውቁኝ አልፈቀዱም፤”ይላል እግዚአብሔር።

7. ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ እንደ ብረት አነጥራቸዋለሁ፤ እፈትናቸዋለሁም፤ስለ ሕዝቤ ኀጢአት፣ከዚህ የተለየ ምን ማድረግ እችላለሁ?

8. ምላሳቸው የሚገድል ቀስት ነው፤በሽንገላ ይናገራል፤ሁሉም ከባልንጀራው ጋር በፍቅር ይናገራል፤በልቡ ግን ያደባበታል።

9. ታዲያ ስለ እነዚህ ነገሮች ልቀጣቸው አይገባኝምን?”ይላል እግዚአብሔር፤“እንደዚህ ዐይነቱንስ ሕዝብ፣አልበቀልምን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 9