ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘሌዋውያን 8:29-34 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት፣ ድርሻው የሆነውን ክህነት የመስጫውን አውራ በግ ፍርምባ ወስዶ የሚወዘወዝ መሥዋዕት በማድረግ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዘው።

30. ቀጥሎም ሙሴ በመቅቢያው ዘይትና በመሠዊያው ላይ ካለው ደም ጥቂት ወስዶ፣ በአሮንና በልብሱ እንዲሁም በአሮን ልጆችና በልብሳቸው ላይ ረጨ፤ በዚህም ሁኔታ አሮንንና ልብሱን፣ ልጆቹንና ልብሳቸውን ቀደሰ።

31. ሙሴም አሮንና ልጆቹን እንዲህ አላቸው፤ “ሥጋውን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቀቅሉት፤ በዚያም፣ ‘አሮንና ልጆቹ ይብሉት’ ተብዬ በታዘዝሁት መሠረት፣ በክህነት መስጫው መሥዋዕት መሶብ ውስጥ ካለው ኅብስት ጋር ብሉት፤

32. የተረፈውንም ሥጋና ኅብስት በእሳት አቃጥሉ።

33. የክህነት መቀበያችሁ ሥርዐት እስከሚፈጸምበት እስከ ሰባት ቀን ድረስ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቆዩ፤ ሥርዐቱንም ለመፈጸም ሰባት ቀን ይወስዳልና።

34. ዛሬ የተፈጸመው ይህ ሥርዐት ለእናንተ ማስተሰረያ እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘሌዋውያን 8